Posts

Showing posts from 2015

Refusal decision of the Holy synod members of Ethiopian orthodox church about Reformist/Tehadiso/Hara tiqa/ service in the name of the church

አሁን እነዚህን አባቶቻችንን ምን እንበላቸው??? የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ልጆቻቸውን በትዕግስት ሰምተው፣ እውነትነትን አጣርተው፣ የእግዚአብሔርን ፍቃድና ፍርድ ለቤተክርስቲያን ያስተላለፉትን የዘመናችንን ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ክቡራን አባቶቻችንን ማበርታትና በዚህም በረከታቸውን ማግኘት ነው፡፡ አሁን ያለንበት ዘመን በጎ አይሉት ክፉ፣ ክፉ አይሉት በጎ ሆነና ብዙ ይነገራል፣ ብዙ ይሰማል፣ ብዙ ይጻፋል፣ ብዙ ይነበባል፣ ብዙ ይታያል ጥቂቱን ግን እንመለከተዋለን፡፡ በተለይም በዚህ ዘመን ላይ ላለን ትውልዶች ፈተናም ካወቅንበት መልካም አጋጣሚም የሚሆኑ በርካታ ነገሮች(ክስተቶች) አሉ፡፡ ለዛሬው ግን የተሃድሶን ስልትና እንቅስቃሴን ማሰቡ በቂያችን ነው፡፡ ምክንያቱም በዚህ አንድ ዘመኑ ክስተት ·          ብዙዎች ተጠቅመዋል፡፡ 1.       በመንፈሳዊ ምዘና ሲታይ አባቶቻችን ከቀድሞው እስከ አሁን በውሳኔያቸው፣ በተለይም በሰሞኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ፍሬው ያማረ ውሳኔ፤ አገልጋዮቻች ብዙዎች እንዲነቁ ተግተው ሰርተዋል፤ በጽሑፍ፣ በስብከት፣ በጸሎት፣ በክርክርም፣ በውግዘትም ሳይቀር የሚችሉትን ለማድረግ ወስነዋል…. ስለዚህም ተጠቅመዋል፡፡ 2.      በስጋዊና  ግዑዝ በሆነ ምዘና ደግሞ በገንዘብና ተከታይ ድሆች የነበሩ አሁን ቢጠሯቸው አይሰሙም፣ ታዋቂ ያልነበሩ ለብዙዎች መውደቅና መሳት ምክንያት ሆነዋል ባይዘልቅም እስካሁን ግን ብዙ ደጋፊና ወዳጅ አፍርተዋል፡፡ከሞትህ በፊት እኔ ልሙት የሚሉ ባለማስተዋል የሚንቀሳቀሱ አጃቢዎችን አፍርተዋል፤ የሚበዙትም በስደት የሚገኙ ምዕመናን ናቸው፡፡ §   እናታችንን...

መናፍቅም ድሮ ቀረ ልጄ???

መናፍቅም ድሮ ቀረ ልጄ??? በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን! እኔ ግን እላሉሁ ·         ስም ድሮ ቀረ!  እነ እሱያውቃል፣ ተስፋነሽ፣ ግሩም፣ እጹብድንቅ፣ ተመስገን፣ …. እረ ስንቱ ምንጥ ስም እንሰማ ነበር አሁንማ ምን ስም አለ….(ያለ ምክንያት ቲቲ ዳዲ ሪች…. ከመባል ውጭ)፡፡ ·         ምግብ ድሮ ቀረ፣ መዝናናት ድሮ ቀረ፣ ምንኩስና ድሮ ቀረ፣ ብሕትውና ድሮ ቀረ፣ አባትነትም እናትነትም ድሮ ቀረ፣ መምሕርነት፣ ተማሪነት፣ መሪነት ተመሪነት ሁሉም ተያይዘው ድሮ ቀሩ …. (በቃ ሁሉም ድሮ ቀረ ብለው በባሕል፣ በወግ መጣስና መጠበቅ አለመቻል ሆድ እየባሳቸው አንድ ሊቅ ነገሩኝ)፡፡ ·         ሌላው ቀርቶ ለማኝነትም ድሮ ቀረ …አሁንም ፈሽን ተከታይ ለማኝ ሀገሪቷን ወሯት አይታይህም አሉኝ፡፡ ... ምን ማለትዎ ነው ስላቸው እነዲህ አሉኝ እስኪ ስማው የሚለምንበት አላማን የሚለምንበት ስምና መንገድ ልመናውን ጨርሶ ሲሳካለት የሚያመሰግንበት መንገድና ቃላት…. (እኮ ፍጹም ኢትዮጵያዊውም ሃይማኖታዊም ሽታ የላቸውም… ዝርዝሩን ለአንተ አሉኝ)፡፡ ·         ግን እኮ….. መናፍቅም ድሮ ቀረ ብለውኝ እርፍ አሉ፡፡ እናንተ ለካ መናፍቅ/ ኢ አማኒም የለም/ አሉኝ …… ወቸ ጉድ ብለው እኛን በክርክር አላስወጣ አላስገባ ያለንን ይህንን ሁሉ መሰረተ ቢስ መናፍቅ  ወዴት ዘነጉት እንድል አደረገኝ፡፡ ለነገሩ አሉኝ እግዚአብሔር ላያስችል አይሰጥም ይባላል አሉኝና የተለመደው...

ይድረስ፤ ለሰማዕታት፣ ለአባቶችና ለቄሳሮቻችን

                      ይድረስ ለእናንተ             ሰማዕታት ለጤናችሁ እንደምን አላችሁ እንዳልል ሰላም ከሌለበት ዓለም በሰላም አባት ክርስቶስ መጠራታችሁን መሪዎቻችንና አባቶቻችን በይፋና በፍጥነት ባይነግሩንም ጠላቶቻችን ገዳዮችና ባዕዳኖች የተባሉ መገናኛ ብዙሃን ነግረውናል፡፡ እናንተየ አዲሱ ቤታችሁ እንዴት ያምር? እንዴት ይደንቅ ይሆን? እንዴትስ የሚያብረቀርቅ የተወደደና የተለየ ዘላቂ ማረፊያ አግኛታችሁ ይሆን? እኔ ምለው ሰማዕታት ለመሆኑ ማነው ያስተማራችሁ?       ማነው ያጠመቃችሁ?       ማነው ያሳመናችሁ?       ማንስ ነው የሰማዕትነትን ዋጋና ጣዕም ያቀመሳችሁ?       ማንስ ነው ዘመኑን አትምሰሉ፣ ወደኋላ አትበሉ፣ የሎጥን ሚስጥ ታሪክ አስታውሱ ያላችሁ?       ማንስ ቄስ ፣ ማንስ ጳጳስ ትጉ በርቱ ጽኑ ብሎ ቡራኬ ሰጣችሁ?       የትስ ኮሌጅ ፣የት ዩኒቨርስቲ የመንፈስ መበርታትን የዓላማ ፅናትን ተማራችሁ …….. ? መልሱን ለውሳጣዊ ነፍሴ መልሱላት(አማልዱኝ)፡፡ እኔ ግን እላለሁ እናንተ ሰማዕታት ንዑዳን ናችሁ, ገንዘብ ብላችሁ ሄዳችሁ ሐይማኖት ገዝታችሁ መጣችሁ, ላንረሳ በልባችን ተፃፈ ስማችሁ እናንተ ሰማዕታት ክቡራን ናችሁ, ኢትዬጵያ ሀገረ እግዚአብሔር መሆኗን ለዓለም መሰከራችሁ፡፡   ...

የዓብይ/የሁዳዴ/የጌታ/ ጾም part 1

የዓብይ/የሁዳዴ/የጌታ/ ጾም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን! ኢዩ 2÷12   “አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ።” ውድ አባቶቻችን፣ እናቶቻችን፣ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ምዕመናንና ምዕመናት እንኳን ለታላቁ የዓብይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡ እናታችን ቅድስት ቤተክርስቲያን በአምላካችንንና በመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከታነጸች ጊዜ ጀምሮ የተለያዩና እጅግ ብዙ የሆኑ ጸጋዎችንና ሐብቶችን ለልጆቿ ስታጎናጽፍ ቆይታለች፡፡ ከእነዚህም ታላላቅ ስጦታዎቿ መካከል በየዓመቱ በናፍቆት የምንጠብቃቸው የዓዋጅ ጾሞች ዋንኞቹ ናቸው፡፡ በዚህ የእውነት ልባዊ መናፈቅ የምንጠብቃቸው የሚሰጡንን የነፍስም የስጋም በረከቶች በማሰብ ነው፡፡ ከላይ በመግቢያችን እንደጠቀስነው እግዚአብሔር በነቢያትን አድሮ ሰው ሁሉ ፍጹም በሆነ የልብ መሰበር፣ መጸጸት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዲገባው አስተምረዋል፡፡ ይህ ደግሞ የሚፈጸመው በጾም በጸሎትና በምጸዋት ነው፡፡ ሰው ከዘላለም ጠባቂያችን እግዚአብሔር መለየት ችሎ ተለይቶ ሳይሆን ኃጢያትን በሰራ ጊዜ ሁሉ ከአምላኩ ጋር ያለውን የረድኤት ግንኙነት በፈቃዱ ያሻክረዋል፣ ያን ጊዜም ከአምላኩ ተለየ ይባላል፡፡ ዘላለማዊ አባቱን የተለየ ሰውም ከእግዚአብሔር እንዲታረቅ ያስፈልጋልና በመጸጸት(ንስሐ በመግባት) ሊጾምና ሊያዝን ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረጋችንም ቀድሞ ለእስራኤል ዘስጋ እንደተነገረ ለእኛ ለእስራኤል ዘነፍሶችም ያስፈልገናልና ጾም የታዘዘው በእግዚአብሔር ነው፡፡ ስለዚህም ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ከእሱ ጋርም ለመሆን ሁል ጊዜ መጾም ያስፈልጋል፡፡ ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን ምዕመናንም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ጾሙን በመጀመርና በመባረክ እኛም እን...