Posts

Showing posts from 2014
Image
+ እንኳን ለጌታችንና ለመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ልደት በሰላም አደረሳችሁ!!!+ ለሚገባችሁ ና ለሚገባች ጓደኞቼ በሙሉ_____________________________________________ 1 ኛ ዩሐ 4 ÷ 9 “በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና፡፡” ይህ የሆነው እከብር አይል ክቡር፣ እነግስ አይል ንጉስ፣ ቅድመ ዓለም የነበረ፣ ማዕከለ ዓለም ያለና ድህረ ዓለም የሚኖር ሁሉን በፈቃዱ የሚያከናውን የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ በቤተልሔም ሲወለድ ነው፡፡ ከዚህ ፍቅረ እግዚአብሔር መገለጥ በፊት ብዙ አባቶቻችን በምግባር ቢቀኑም ብዙ ነቢያቶችም በትንቢት ቢተጉም ይህን የተከበረ የአምላክ ሰው መሆን ምስጢር በምሳሌና በትንቢት መነጽር አይተውታል እንጂ አልደረሱበትም ፤ ‘’እኛ ግን ዳሰስነው፣ አብረነውም በላን፣ ጠጣን… ይህን የተመለከቱ አይኖቻችሁ፣ ይህን የሰሙ ጆሮዎቻችሁ ብጹዓን ናቸው’’ እንደተባለ፡፡ ይህ የአምላክ ሰው መሆን ልዩ እና ታላቅ ፍቅር ለሰው ልጅ የተገለጠው በእግዚአብሔር በጎ ፍቃድና በሰው ልጆች ሁሉ አባት አዳም ንስሐ መግባት ምክንያት ነበር፡፡ የመገለጡም ዓላማ v   ኃጢአትን መሻር ዕብ 9 ÷ 26 ዩሐ 3 ÷ 16 v   የአዳምን የቀደመ ክብሩን መመለስ ገላ 4 ÷ 7 v   ለአዳም ልጆች ምሳሌ ሊሆነን ብሎ ዳግማዊ አዳም ከርቀት ወደ ግዝፈት፣ ከምልዑነት ወደ መወሰን መጥቶ የተሰወረ የመለኮትን ነገር አሳወቀን፡፡ ማቴ 3 ÷ 16፣ የጨለማ ዘመን ያበቃባት ብርሃን የተገለጠባት ያች የኤፍራታ አውራጃ ቤተልሔምም ቅዱሳን መላዕክትና ሕጻናት በአንድ ቃል የጥል ግድግዳ መፍረሱን ...
Image
የሀና ደፋሪዎች ከየት መጡ!? የሚከተሉት ሰዎች እህታችንን የምድር ቆይታዋን ቀጩባት ያሳዝናል፡፡ ሀና ፍርድ በዚያ አለ፣ እውነት በዚያ አለ፣ አምላካችንም መልክ፣ ስልጣን፣ ቁመና፣ ገንዘብ፣ ዝና …. ሌሎችም ሁሉ ለፍርዱ የማይጠቀም ነውና ፍርድ ታገኛለሽ፡፡ ይሁን እንጂ እኚህ ክፉ አውሬዎች ጨከኞችና ከሀዲዎች ያደረሱብሽን ባልናገር ከበደኝ እናም ላጋልጣቸው ተነሳው፡፡ እኔ ምለው አንተ አንባቢ ደሞ ለምን፣ ማን፣ እንዴት ተደፈረች ትላለህ/ሽ/ ? አታፍርም እንደማያውቅ ሰው ታስመስላለህ ? ግፍ አይሆንብህም፣ ህሊና አልህ ግን ? ስማኝ ልጠቁምህ ሀናን የደፈራትን ያዋረዳትን ያን ሰው መሰል ፍጡር፣ ሰው ነኝ ባይ ፍጡር አውቀዋለሁ/አውቃቸዋለሁ/ አውቅሃለው፡፡ እኔ ግን እላለሁ እነዚህ ደፋሪዎችና ሰው ብቻ ሳይሆን እንሰሳም መሆን ያቃታቸው፣ ኢትዮጰያዊ ያውም ጎረቤቶቻችን እነ እንትና/እነ እገሌ/ ናቸው፡፡ ለማስለፍለፍ ፈልጋችሁ ካልሆነ እናንተ አንባቢያኖች ሁላችሁም ታውቓቸዋላችሁ እረ እንደውም እናንተም ራሳችሁ ተባባሪ ነበራችሁ አውቃሁ፡፡ የማላውቅ መስሏችሁ እንጂ አውቃለሁ፣ ያልሰማው መስሏችሁ እንጂ ሰምቻለው፣ ያላየው መስሏችሁ እንጂ አይቻለው፡፡ መቼስ የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያድርቅ አይደል የሚባለው፤ ከዘበዘባችሁኝማ አውነቱን ላወጣ ነው፣ እውነተኛ ዳኛ ይዳኘን ብዬ፡፡ ለነገሩ ፍርዱም የተበላ ዕቁብ ሆኗል አሉ፣ ራስን የማያውቅ ዳኞች ናችሁ አሉ፣ እውነትን ሳይሆን ክብርን፣ ገንዘብን፣ መወደድን፣ ስልጣንን….. የምታሯሩጡ ቀማኛ ናችሁ አሉ፡፡ እናም ልንገራችሁ እንጂ እናንተስ ፍርድ አታውቁም፣ ፍርዳችሁም ኦርዮን እንዲገደል መሆኑን አውቃለሁ፡፡አይ አንተ ኦርዮን ሚስትህንም፣ ፍቅርህንም፣ ህይወትህንም የተነጠክ ምንኛ ፍርድ ተጓደለብህ ??? ፍርድ ...
Image
Dear all In the name of the father the son and the holly sprite one God. Amen! I wanna to give many thanks to you who spent time on reading this blog. I expect that many of us favor to funny things in our life but this blog may not only on delivering comical things to the reader rather i am sure that you will  acquire at least new side of looking to things and phenomenon.  Through out our journey you will enjoy to my view of mainly on spirituality and solution pointing for many troubles of to this beloved mother land Ethiopia. For these all above objectives succession please don't forget to call my name on praying.     Wait    Thank you